[ አውቃለሁ]

aweqaalahu

The things we don't say out loud but known to the heart

ቆንጆ ሴት ውብ እንስት አይደለሁ አውቃለሁ

አይኖቼም ጨረቃን አይመስሉም አውቃለሁ

ፀጉሬ ሀር እንዳይደል ይሄንን አውቃለሁ

ፈገግታየዬም ብርሃን እንዳይረጭ አውቃለሁ

ባትወደኛ ኖሮ ባጠገብህ ባልፍ 

ዞረህ ቆም ብለህ አታይም አውቃለሁ

ለእናትህ ስትነግራት ፎቶዬን ስታሳያት

አመለ ሸጋ ናት ስነስርአት ያላት 

ጨዋ ያሳደጋት

ብለው እንዳለፉ ባልሰማም አውቃለሁ

ለጓደኞችህም ሳታሰተዋውቀኝ

3ቱን ወር ትምህርቴን

3 ቱን ወር ፀባዬን 

እግዜሩን መፍራቴን

ስትነግር እንደከረምክ ሳትነግረኝ አውቃለሁ

ሲያዩት ያላማረ ብለዉ እንዳይተፋኝ

በብዙ እንደደከምክ ይሄንን እረዳለሁ

ያገር ምድሩ ባለ ቅኔ ስለ ቆንጆ ሲቀኝ

ግጥም ሲደረድር ዜማውን ሲሰድር

ልትጋብዘኝ ወደህ ሁለቴ አስበህ

ስንኙን መርምርህ

እንደምትተወው

ባትልም አውቃለሁ

ግን አብረን ስንሆን

 በጨዋታ መሀል 

አለ አይደል አንዳንዴ

እኔን ደስ እንዲለኝ

ታምሪያሽ ግን በለኝ

Comments (2)
No comments yet